- Post:ICT
- Tuesday, November 11, 2025
- Read 289
- 289
- 265
ዜና ሻሎም
ሻሎም ቢዝነስ እና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ በማስተርስ፣ በመጀመሪያ ድግሪ እና በዲፕሎማ መርሀ ግብር ሲያስተምራቸው የነበረውን በርካታ ተማሪዎቹን በዛሬው ቀን ነሀሴ 17/2017 ዓ.ም በሴንትራል ሆቴል ሀዋሳ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተመራቂ ተማሪ ቤተሰቦች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ለአምስተኛ ጊዜ አስመርቋል። በዕለቱ የሻሎም ቢዝነስ እና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፀጋዬ ማቴዎስ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈው በንግራቸውም ተመራቂ ተማሪዎች በቀጣይ ምዕራፋቸው በተመረቁበት የትምህርት መስክ ሀገራቸውን በታማኝነት በትጋት እንዲያገለግሉ መልክታቸውን አስተላልፈዋል። እንዲሁም የሲዳማ ብሔራዊ ክልል መንግስት ብቃት ምዘና ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ቴዎድሮስ ገቢባ በክብር እንግድነት ተገኝተዋል። አቶ ቴዎድሮስ በምረቃው ተገኝተው ተመራቂ ተማሪዎች ት/ት በዚህ የማያበቃ ትኩረት የሚሻ ጉዳይ እንደሆነ ፣ ተመራቂ ተማሪዎች ማንኛውንም ስራ ተግተው እንዲሰሩና ቤተሰብን እና ሀገርን እንዲወዱ ምክር አዘል የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። በተጨማሪም የክብር እንግዳው ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች የሜዳሊያ እና የዋንጫ ሽልማት አበርክተዋል። ሀዋሳ፣ ሲዳማ፣ ኢትዪዺያ።